Friday, July 3, 2015

ቤተክርስትያኗ በአይ ኤስ ለተገደሉ ወገኖች ቤተሰቦች ድጋፍ አደረገች




 አዲስ አበባ ሰኔ 25 2007 (ኤፍ ) በስዊዘርላንድ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በአይ ኤስ ለተገደሉ ወገኖች ቤተሰቦች 400 ሺህ ብር በላይ ስጦታ አበረከቱ። ድጋፉ የተደረገው 11 ተጎጂ ቤተሰቦች ሲሆን፥ ለእያንዳንዳቸው 27 ሺህ 500 ብር በአጠቃላይ 400 ሺህ ብር በላይ ተብርክቶላቸዋል። እጅግ ችግረኛና በእድሜ ለገፉ ስድስት ቤተሰቦችንም ለመደገፍ ቃል ገብተዋል። የቤተክርስትያኗ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ባስተላለፉት መልዕክት ቤተክርስትያኗ ይሄን አሰቃቂ ድርጊት ከሰማችበት ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ተግባራት አከናውናለች።

የተፈጸመው አሰቃቂ ድርጊት ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ምንም ዋስትና ወደ ሌለበት አገራት እንዳይሰዳዱ ትልቅ ትምህርት ነው ያሉት ብፁእነታቸው በቀጣይም ቤተክርስትያኗ ዜጎች በአገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ ትሰራለች ብለዋል።ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የተወከሉት አምባሳደር ሙሌ ታረቀኝ በበኩላቸው መንግስት ችግሩን ከምንጩ ለመድረቅ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል።

ምንጭ:-ኢዜአ

No comments:

Post a Comment