Friday, August 18, 2017

ምሥጢረ ደብረ ታቦር


 ዲያቆን መልአኩ እዘዘው
በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ

እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለ
የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ። ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር። ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና። ተነሡ አትፍሩም አላቸው።ዓይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም። የማቴዎስ ወንጌል 171-8
በቂሳርያ ጌታችን ለደቀመዛሙርቱ ለሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ብሎ ጠይቋቸው አንዳንዶች ከነቢያት አንዱ ነህ ይሉሃል፣ አንዳንዶች ሙሴ ነህ ይሉሃል፣ ሌሎች ደግሞ ኤልያስ ነህ ይሉሃል እያሉ መለሱለት ጌታችንም መልሶ እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ ብሎ ሲጠይቃቸው የሐዋርያት አፈጉባዔ ሊቀ ሐዋርያት /ጴጥሮስአንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ነህብሎ በመመስከሩ ጌታምየዮና ልጅ ስምዖን ሆይ በሰማይ ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ…› ተብሏል፡፡

የዘመናችን ፈተና… … … .‹‹አብያተ ክርስቲያናትን ማፍረስና ማቃጠል …..››



(አንድ አድርገን ነሐሴ 12 2009 ዓ.ም)፡- ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታ ውስጥ ብቻ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ላይ በየጊዜው የሚደርሱት ጫናዎች ከቀን ቀን ፤ ከዓመት ዓመት እየጨመሩ ይገኛሉ ፡፡ በአጽራረ ቤተክርስቲያን አማካኝነት በውድቅት ሌሊት ከሚፈርሱ እና ከሚቃጠሉ አብያተክርስቲያናት እንስቶ ፤ መንግሥታዊ ሥልጣንን ፤ ሕዝብን ለማስተዳደር የተሰጣቸውን ጊዜያዊ አስተዳደራዊ ጡንቻን በመጠቀም በመዲናዋ አዲስ አበባ አንስቶ እስከ ሀገሪቱ ጠረፍ ድረስ በየጊዜው የሚፈርሱት እና የሚነሱት አብያተ ክርስቲያናት እየጨመሩ መምጣታቸው አሁን ላይ አሳሳቢ ጉዳይ ሆኖ ተገኝቷል ፡፡ ለመፍረስ ቀን የተቆረጠላቸው ፤ የፈረሱ ፤ የተቃጠሉ ፤ ዶዘር የታረሱ አብያተ ክርስያናት የምዕመኑን ፤ የቤተክርስቲያኒቱን ሕልውና አደጋ ላይ እየጣሉ ይገኛሉ፡፡ እስኪ ይህን እውነታ በመረጃ ለማጠናከር ከዚህ በፊት ከ2002 ዓ.ም በኋላ በአንድም በሌላም መንገድ አብያተ ክርስቲያናት ላይ የደረሰውንና እየደረሰ የሚገኝውን  አደጋ ለመመልከት እንሞክር፡፡